top of page

Poem by Zufan Lemma



የሃዘን እንጉርጉሮ

እንቧ ይላል በሬ አጣማጁን ሲያጣ

በቃኝ ብለህ ስትሄድ እንዴት አንጫጫ!

ታሪኳን መዝጋቢ ኢትዮጵያ ስታጣ

አንተን የመሰለ ዐዋቂ ጠበቃ

አጣች መከታዋን እምዬ ኢትዮጵያ።


አንጋፋው መምህር የብዕሩ ጀግና

የወጣቱን ትውልድ ተክተሃልና

አሻራህ ይኖራል እስከ ዓለም መጨረሻ

የኢትዮጵያዊነታችን ተምሳሌት መግለጫ።


እኛም ዘመዶችህ ያልጠገብንህ ገና

ይሻልሃል ብለን ስንጠብቅ በተስፋ

ሆነብን ሃዘንህ እንደ እሬት መራራ

ጉዞህን አሳመርክ ዳግመኛ ላትመጣ።


በል ደህና ሁንልን የሸንኮራው አርበኛ።

ሰላምታ አድርስልን ለአብዬ ሃይሌ ለሺመቤት ዲና


ጋሼ ጌታቸው ነፍሥህን በአጸደ ገነት ያኑርልን።


- ዙፋንሽ ወርቅ(ዙፋን) ለማ


5 views0 comments
bottom of page